አያይዘን አንድ አድርገን እንዳንጠፋ ተነካክሰን ቃየን ወንድሙን ገደል ጌታ መስዋዕቱን ስላልተቀበለ ልቡ በቅናት ተሞልቶ ለጥፋት ተነሳ ጭካኔ ተሞልቶ ዛሬም እንደ ቃየን አለ እንደገና ለምን ተሳካለት ብሎ የሚቀና ሰይፍ ይዟል በእጁ አፉ እንደማር ጉድጓድ ይቆፍራል ገድሎ ሊቀብር አያይዘን አንድ አድርገን እንዳንጠፋ ተነካክሰን ከሁሉ መጀመሪያ የታዘዝኩት ፈቃድ እንኳን ወንድሚንና ጠላቴን እንድወድ እጃችን ተያይዞ ልባችን ተራራቀ ከየት ፈውስ ይመጣል መርዙ ከተደበቅ አያይዘን አንድ አድርገን እንዳንጠፋ ተነካክሰን በቤትህ ውድድሩ በዛ እኔ ልታይ ልታይ እኔ ብቻ ልግዛ ቃልህን የሚሰብከው ሞልቶ እንደሚናገረው ይሚኖረው ጠፍቶ ነብይ አስተማሪ ሁሉ ጐራ ይዞ ሰይፍ ይማዘዛል እዛ እዚህ ማዶ አካል ተበታትኖ ዓይኖረውም ውበት ማን ክብርህን ወስዶ ይኖራል በሕይወት አያይዘን አንድ አድርገን እንዳንጠፋ ተነካክሰን ከሁሉ መጀመሪያ የታዘዝኩት ፈቃድ እንኳን ወንድሚንና ጠላቴን እንድወድ እጃችን ተያይዞ ልባችን ተራራቀ ከየት ፈውስ ይመጣል መርዙ ከተደበቅ የህግ ሁሉ ፍጻሜ የትዛዛትም ሁሉ መጀመሪያ ባልንጀራህን እንደ እራስህ አድርገህ ውደድ ብለኸን የቤትህ ማገርና መሰሶ የሆነውን ፍቅርን ጥለን ፍቅርን ስንገፋት ስትወጣ ከቤቷ እግሯን ተከትሎ ገባ ያ ጠላቷ ማናከስ ጀመረ እንድንጠፋፋ አደባባይ ወጥተን እንድንገፋፋ ሰው አካሉን መብላት መንከስ ከጀመረ መገመት ይቻላል ምን ሊሆን እንዳለ አወይ ጉድ ሆነናል ወገን ተው እንንቃ ፍቅር በሊለበት እርሱም የለም ለካ አያይዘን አንድ አድርገን እንዳንጠፋ ተነካክሰን