ደግሜ ደግሜ ብደጋግም የማይሰለቸን ሁሌ ብዘምር አሁንም መልሼ ብደጋግም የማይሰለቸኝ ሁሌ ብዘምረ የመዳኔ ነገር ቀሎ ስለመጣ አይቀልም በሕይወቴ የመስቀሉ ስራ በክብር ታጅቦ ይመጣል ሊወስደኝ እርጐኛል ሙሽራ ሰማይ ደስታ ሆነ ዕልልታው ቀለጠ በእኔ መዳን እንዴተ መታደል ነው በበጉ ዙፋን ፊተ ከእርሱ ጋር መሆን አጋንንት ቢወጣ ሽባ ቢተረተር የሞተ ቢነሳ ይህም ያልፋል ምድር አይወዳደርም ይሄኛው ተአምር የመዳኔ ነገር ደግሜ ደግሜ ብደጋግም የማይሰለቸን ሁሌ ብዘምር አሁንም መልሼ ብደጋግም የማይሰለቸኝ ሁሌ ብዘምረ የመዳኔ ነገር አማኝ ሞት አይፈራ እንግዳ ነውና በዚህ ምድር ላይ ይናፍቃል እንጂ ከአምላኩ ጋር መኖር በላይ በሰማይ ሰው ዓለምን ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢያጐድል መቼ ይጠቅመዋል ከክርስቶስ ጋራ ለዘላልም መኖር ከሁሉም ይበልጣል ጠላቴ ሆይ ስማ ሞኝህን አሰፈራራ ሞት እይፈራም አማኝ ሰማይ የእርሱ ስፍራ ይሄ አለኝ ብዬ ቁሳቁስ አልቆጥር የእኔ ሃብት ይሄ ነው ሞትን የሚሻገር የመዳኔ ነገር ክብር ቢሆን ያልፋል ዝና ቢሆን ያልፋል ጉልበት ቢሆን ያልፋል ሃዘን ቢሆን ያልፋል ማግኘት ቢሆን ያልፋል ማጣት ቢሆን ያልፋል የማያልፈው አንድ ነገር በሰማያት ያለ ክብር ተጽፎልኝ ስሜ በላይ ከዚህ በላይ ደስታ አለ ወይ በዚህ ነው የእኔ ደስታ ሞልቶኛል ዕልልታ ለዚህ ነው ጩኸቴ ሰማይ ቤት በመግባቴ ክብር ቢሆን ያልፋል ዝና ቢሆን ያልፋል ጉልበት ቢሆን ያልፋል ሃዘን ቢሆን ያልፋል ማግኘት ቢሆን ያልፋል ማጣት ቢሆን ያልፋል የማያልፈው አንድ ነገር በሰማያት ያለ ክብር ተጽፎልኝ ስሜ በላይ ከዚህ በላይ ደስታ አለ ወይ