ንፋሱ ነፈሰና አለፈ ወጀቡም ጸጥ አለ አለፈ መንገዴን ዞር በዬ ሳየው ይህ ሁሉ ለመልካም የሆነው ስላለ ጌታ አጠገቤ ስላለ አባ አጠገቤ ከኖሩማ ኑሮ ከአንተ ጋራ በችግር ቢሆን በመከራ ከተያዘም እጄ በአንተ እጅ ሕይወቴ ሰላም ነው የሚመች ስሄድ ከአንተ ጋራ በሕይወት መንገድ ምንም ነገር አይሆን ያለ አንተ ፈቃድ አያስጨንቀኝም ነገ የሚሆነው የነፍሴ ፍጻሜ በእጅህ ነው የእኔ ነገር ሰው ይማይዘጋው ሰው የማይከፍተው ሁሉ በእጁ ነው የእኔ ነገር መጀመሪያዬ መጨረሻዬ በእርሱ አይደል ወይ ከኖሩማ ኑሮ ከአንተ ጋራ በችግር ቢሆን በመከራ ከተያዘም እጄ በአንተ እጅ ሕይወቴ ሰላም ነው የሚመች ሲጸልይ ዳናኤል አንተን ስለጠራ ጉድ ጓድ ውስጥ ከተቱት በአንበሳ እንዲበላ ይንከባከቡታል እንኳን ሊበሉት ችግር ይቀየራል በምቾት የእኔ ነገር ሰው ይማይዘጋው ሰው የማይከፍተው ሁሉ በእጁ ነው የእኔ ነገር መጀመሪያዬ መጨረሻዬ በእርሱ አይደል ወይ ቆይ ምን አለ ከአንተ የራቀ የተሰወረብህ እኮ ምን አለ አልፋ ኦሜጋ ሁሉን የምታውቅ ቆይ ምን አለ ድንገት ተገልጦ የሚያስደነግጥህ እኮ ምን አለ ሰማይ ምድሩን ሁሉን በእጅህ ይዘህ መላ ሕይወቴ አምላኬ ሁሉ በእጅህ እድሜ ዘመኔ አምላኬ ሁሉ በእጅህ ነገዬም ቢሆን አምላኬ ሁሉ በእጅህ እስትንፋሴ እንኳን አምላኬ ሁሉ በእጅህ