በመንገዴ ስሄድ ስራመድ በሕይወት ጐዳና እግሮቼ በቤትህ ጸንተው ዓይኔ ግን ሳይበራ የሚሄደው የሚመጣው ሲያዳክመው ልቤን የቆምኩኝ ያለሁኝ መስሎኝ እያንገዳገደኝ አልገባኝም ነበር የልቦና ዓይኔ ታውሮ ምድር ምድር አለ የከበረውን ሰማይን ጥሎ ቃልህን ስሰማ ልቤ ተደስቶ ለጊዜው ነበረ በስሜት ተገፍቶ ነፋስና ጐርፉ ሊፈትነኝ መጣ ይታወቀኝ ጀመር ከመንገድ ስወጣ ቢበራማ በቃልህ ቢጸና ዓይኔ ቢበራ ቢበራማ ጸንቶ ይቆም ነበር ፍሬ እያፈራ ቢበራማ ቅርንጫፍ ከግንዱ ከተጣበቀ ቢበራማ ያስታውቃል መልኩ አንተን ያወቀ ዓይኖቼን አብራ ክፈት ዓይኔን እነደ እኔ ሳይሆን እንዳንተ እንዳይ በመንገዴ ስሄድ ስራመድ በሕይወት ጐዳና እግሮቼ በቤትህ ጸንተው ዓይኔ ግን ሳይበራ የሚሄደው የሚመጣው ሲያዳክመው ልቤን የቆምኩኝ ያለሁኝ መስሎኝ እያንገዳገደኝ አልገባኝም ነበር የልቦና ዓይኔ ታውሮ ምድር ምድር አለ የከበረውን ሰማይን ጥሎ ሲዘነጋ ለቤ የሰማዩን ቤቱን በዚህ ምድር ፡ሲኖር እንግዳ መሆኑን አይጐመጅም ነበር ለምድራዊው ኑሮ የሰማዩን ዓለም አንዴ ቢያየው ኖሮ ቢበራማ የተጠራበትን የክብር ተስፋ ቢበራማ የዘላለም እርስት ከቶ ማይጠፋ ቢበራማ ዓይኖቼ ተከፍቶ ይህንን ቢያይ ቢበራማ ይናፍቃል ልቤ ወደ ሰማይ ዓይኖቼን አብራ ክፈት ዓይኔን እነደ እኔ ሳይሆን እንዳንተ እንዳይ ልመናዬ ይሄ ነው አብራው ዓይኔን