የመጣው ፈተና ከአቅሜ በላይ ከቶ አያስቀረኝም ከመንግስተ ሰማይ የገሃነም ደጆች አይችሉኝምና ኃይል አለኝ ዛሬም ሄዳለሁ ጥሼ ጥሼ ገና ከገጠመኝ ዉጊያ ከጠላት ፈተና ጌታ አሻገረኝ ሁሉን ቻይ ነውና በደከምኩኝ ጊዜ ቆሞ ከአጠገቤ አትፍራ ስላለኝ ብርቱ ሆኗል ልቤ ብርቱ ሆኗል ልቤ*4 አሻገረኝ*3 ጌታ አሻገረኝ አሻገረኝ*3 ጌታ አሻገረኝ ጌታ አሻገረኝ *3 አለሁልህ እያለኝ ጌታ አሻገረኝ *3 አለሁልህ እያለኝ ሕይወት ሆኖለታል ለደረቁ አጥንቴ ብርታት ለቆበታል በዛለው ጉልበቴ ማን ነበርኩኝ እኔ ባይረዳኝ አባቴ በርሱ ፀንቶ ቆሟል ያዘመመው ቤቴ ያዘመመው ቤቴ*4 እኔ አለሁ በጤና*6 ሞቴን የተመኘው ጠላቴ ሲበላ ከአመት ዓመት ከዘመን ዘመን በሰላም ጠብቆ ያሸጋገረኝ መድኃኒዓለም ከፍ ይበልልኝ *9 ጠላት ሲያባርረኝ ሊይዘኝ ከኋላ በትር ስዘረጋ ተገኝቶኛል መላ በደረቁ ምድር እኔን አሳልፎ የሚከተለኝን ጠላት ሬሳውን አንሳፍፎ ሬሳውን አንሳፍፎ*4 ለቅሶ ዋይታ እንዲሆን ሁሌም በእኔ ቤት ሲሟርት ሲመትት እንዳልኖር እንድሞት ጨርቁን ጥሎ አበደ ሞቴን የተመኘ የበቀል ዘመን ነው ለካ የመሸጋገሬ እኔ አለሁ በጤና*6 ሞቴን የተመኘው ጠላቴ ሲበላ ከአመት ዓመት ከዘመን ዘመን በሰላም ጠብቆ ያሸጋገረኝ መድኃኒዓለም ከፍ ይበልልኝ *9 ላሻገረኝ ለዚህ ጌታ ምስጋናዬ ለርሱ ይግባ ላበሰልኝ የአይኔን እማባ አምልኮዬ ለርሱ ይግባ ለርሱ ይግባ *4 ለዚህ ጌታ ለርሱ ይግባ *4