ክበር የሆነን ጌታ ሞገስ የሆነን ጌታ ብቃት የሆነን ጌታ በጉድለታችን ፈንታ ክንዱን በዘመናችን በዓይናችን አይተነዋል መልካም እረኛ ኢየሱስ እስከዛሬ ረድቶናል በዘመን በአመታት መሃል የሚገዳደረው የታል ብቻውን ድንቅ እየሰራ የሚኖር እንደተፈራ ለእኛም ይሄው ሞገስ ሆነን ባሕሩን ከፍሎ አሻገረን ችግራችንን እረሳነው በኢየሱሱ ስንቱን አለፍነው አዝ ክበር የሆነን ጌታ ስንቱን ተሻገርንአለፍን በምሥጋና ሆ እያልን ስንቱስ ከእግራችን ወደቀ በኢየሱስ እይደቀቀ ዘመን ሲያልፍ ዘመን ሲተካፍሬያችንአብቦ ፈካ የረገጥነውን ወረስን እለት እለት አማረብን አዝ ሞገስ የሆነን ጌታ በምድረ በዳ በረሃ የሚያረካ ውኃ ሆነን አልሰለቸን የእኛ ጌታ እንደቃሉ ተለመነን በመከራ ቀን ሰቀቀን ተማምነን ስሙን ስንጠራ ደረሰልን በስአቱ ኢየሱስ ጌታ የሚያኮራ አዝ ክብር የሆነን ጌታ ሸንጐ በእኛ ላይ ሲማከር ዲያብሎስ ሊያጠፋን ሲጥር ማነው ደርሶ የታደገን መርከብ ሆነን ታሪክ ይናገር ብዙ ብዙ ነው እኛስ ያለፍነው በእግራችን ስር ወድቆ ጠላት ጭንቅላቱን ረገጥነው አዝ ክበር የሆነን ጌታ