ሄኖክ ሞትን እንዳያይ በእምነት ተወሰደ ኖህ በምድረ በዳው መርከብን አበጀ አብረሃም እርስቱን ከነዓንን ወረሰ ሳራም በእምነቷ ኃይሏ ተመለሰ አዝ፦ ጻድቅ ግን በእምነት በሕይወት ይኖራል የሚታየውን ሳይሆን የማይታየውን ይረዳል የተስፋውን ቃል የሰጠው የታመነ ነውና ደካሞች በእምነት ጉልበታችሁ ይጽና (2x) ነፍሱ ፍፁም ደክማ ትንፋሽ ተሰውሮ የሚታይ መመኪያ ከአፈር ተቀብሮ ሥጋ ደግሞ ዝሎ ሞት ሽታ ሲሸተው ጻድቅ ግን በእምነት ከክርስቶስ ጋር ነው አዝ፦ ጻድቅ ግን በእምነት በሕይወት ይኖራል የሚታየውን ሳይሆን የማይታየውን ይረዳል የተስፋውን ቃል የሰጠው የታመነ ነውና ደካሞች በእምነት ጉልበታችሁ ይጽና (2x) ባሕሩን በበትር አሻግሮ የከፈለ ውሃን እንደ ግድግዳ ገትሮ ያቆመ ዝናብን ኤልያስ በእምነት ከለከለ እስራኤል በአምላኩ ጉልበቱ አየለ አዝ፦ ጻድቅ ግን በእምነት በሕይወት ይኖራል የሚታየውን ሳይሆን የማይታየውን ይረዳል የተስፋውን ቃል የሰጠው የታመነ ነውና ደካሞች በእምነት ጉልበታችሁ ይጽና (2x)