አዝ፦ የኃያላን ኃያል የእኛ ጌታ በሰልፍ በወጀቡ የበረታ እንደ እርሱ የሆነ/የሚሆን ማንም የለም ይክበር ይንገሥ ለዘላለም (2x) ብዙ ሃያላኖች በምድር ላይ ነበሩ እንድ ዘመን ታይተው ጠፍተው በዚያው ቀሩ የእኛ ኢየሱስ ግን መቃብር ፈንቅሎ ከበረ በሰማይ አሜን በሞት ላይ አይሎ አዝ፦ የኃያላን ኃያል የእኛ ጌታ በሰልፍ በወጀቡ የበረታ እንደ እርሱ የሆነ ማንም የለም ይክበር ይንገሥ ለዘላለም የኃያላን ኃያል የነገሥታት ንጉሥ ማነው የሚመስለው የናዝሬቱን ኢየሱስ ማህተቡን ሊፈታ የቻለው እርሱ ነው ይክበር ዛሬም አሜን አዎ ኢየሱስ ጌታ ነው አዝ፦ የኃያላን ኃያል የእኛ ጌታ በሰልፍ በወጀቡ የበረታ እንደ እርሱ የሚሆን/የሆነ ማንም የለም ይክበር ይንገሥ ለዘላለም (2x) ማንም ያልቻለውን መጋረጃ ቀዶ ወንጌልን ሰበከ ወደ ሲኦል ወርዶ ለታሰሩት ሰላም መፈታት አወጀ በመስቀል ላይ ሞቶ በደሙ እኛን ዋጀ አዝ፦ የኃያላን ኃያል የእኛ ጌታ በሰልፍ በወጀቡ የበረታ እንደ እርሱ የሚሆን ማንም የለም ይክበር ይንገሥ ለዘላለም የኃያላን ኃያል የእኛ ጌታ በሰልፍ በወጀቡ ኃያል ንጉሥ እንደ አንተ የሆነ ማንም የለም ክበር ንገሥ ለዘላለም አጋንንት በሥሙ ይታዘዙለታል ሰማይ ምድር ሁሉ ለክብሩ ዝቅ ይላል ማዕበል ወጀቡን ባሕሩን ይከፍላል ጌት ነው ኢየሱስ አዎ ዘለዓለም ይገዛል አዝ፦ የኃያላን ኃያል የእኛ ጌታ በሰልፍ በወጀቡ የበረታ እንደ እርሱ የሆነ ማንም የለም ይክበር ይንገሥ ለዘላለም (2x) እንደ እርሱ የሆነ ማንም የለም ይክበር ይንገሥ ለዘላለም እንደ አንተ የሆነ ማንም የለም ይክበር ይንገሥ ለዘላለም