ጠላቴ ያሻውን ቢያወራ አልሰማም እንኳንስ ልፈራ አምላኬ ጥላ ስር አድራለሁ አስተማማኝ ጋሻ አግኝቻለሁ ዲያቢሎስ ቢፎክር ቢያወራ አልሰማም እንኳንስ ልፈራ አምላኬ ጥላ ስር አድራለሁ የሚያኮራ አባት አግኝቻለሁ አዝ፦ አግኝቻለሁ አባት አግኝቻለሁ (4x) ደሙ በጉ በኔ ላይ ስላለ ጥፋት መቼም አያገኘኝ እንደ ዐይኑ ብሌን ይጠብቀኛል እግዚአብሔር መቼም አይተወኝ ያ የጨለማ ዘመን አለፈ አበቃ ብርሃን በራ አሻገረኝ በበረታች ክንዱ ነፃ ወጣሁ በአምላክ ስራ ፈርዖን ከኋላ ቀይ ባሕር ከፊቴ ከብቦኝ ቢደነፋ ቢፎክር ጠላቴ እግዚአብሔር ሲነሳ ጠላቶቼ ሁሉ በሰባት መንገድ ይበታተናሉ ኃያሉ ሲነሳ የከበቡኝ ሁሉ በሰባት መንገድ ይበታተናሉ ምድሩን ማዕበሉን አልፈራ እግዚአብሔር በኃይሉ አለ ከእኔ ጋራ በአምላኬ እተማመናለሁ ጠላቴ ይሰጥማል እኔ እሻገራለሁ አዝ፦ አግኝቻለሁ አባት አግኝቻለሁ (4x) ማዕበል ወጀቡ ቢነሳ ተራራው ቢገተር ከፊቴ ሁሉም ትክክል ይሆናል ትዕዛዝ ሲወጣ ከአባቴ መድኃኒቴ ከእኔ ጋር ነው አልፈራም እተማመናለሁ እባቡን እና ዘንዶውን እረጋግጬው አልፋለሁ ሰይጣን ተማምሎ ሊያጠፋኝ ቢነሳ ሊውጠኝ ቢጐመጅ ዙሪያዬን ቢያገሳ ልቤ አይደነግጥም በከንቱ ፉከራ እግዚአብሔር ጋሻዬ አለ ከእኔ ጋራ ልቤ አይደነግጥም በከንቱ ፉከራ እግዚአብሔር አባቴ አለ ከእኔ ጋራ ከእኔ ጋራ አለ ከእኔ ጋራ ከእኔ ጋራ አምላክ ከእኔ ጋራ ከእኔ ጋራ አለ ከእኔ ጋራ ከእኔ ጋራ ጌታ ከኔ ጋራ ፈርዖን ከኋላ ቀይ ባሕር ከፊቴ ከብቦኝ ቢደነፋ ቢፎክር ጠላቴ እግዚአብሔር ሲነሳ ጠላቶቼ ሁሉ በሰባት መንገድ ይበታተናሉ ኃያሉ ሲነሳ የከበቡኝ ሁሉ በሰባት መንገድ ይበታተናሉ ወጀቡን ማዕበሉን አልፈራ እግዚአብሔር በኃይሉ አለ ከእኔ ጋራ በአምላኬ እተማመናለሁ ጠላቴ ይሰጥማል እኔ እሻገራለሁ አዝ፦ አግኝቻለሁ አባት አግኝቻለሁ (8x)