ከአንተ ወዴት ወደማን ወዴት እሄዳለሁ (2x) ድምጽህን ሰምቼ አንዴ ተደላድያለሁ የሕይወት ቃል አለ በአንተ ሕይወት አግኝቻለሁ ሰለቸኝ ደከመኝ አታውቅ እኔ አይቼሃለሁ ታዲያ ከእቅፍህ ወዴት ወዴት እሄዳለሁ አባት ቢሉት የደረሰላቸው ፍቅር ሚሉት የቀመሱት ናቸው ተስፋ ጠፍቶ ተስፋ የሆናቸው በተዐምራት በድንቅ የመራቸው አመስግኖ አይጠግብም ልባቸው (2x) ክበር ብሎ ንገሥ ብሎ (አሜን) ልዩ ብሎ አይጠግብም ልባቸው (2x) ያየሁትን የሰማሁትን (የሰማሁትን) እናገራለሁ ያረፍኩበትን (ያረፍኩበትን) (2x) ሞተና በሶስተኛው ቀን ተነሳና ሞተና በሶስተኛው ቀን ተነሳና ነፃ አደረገኝ ዕዳዬን ከፈለና ቀኑን ሙሉ በፍቅርህ በቤትህ እኖራለሁ (2x) በሚያስተማምነው ክንድህ በእርሱ ላይ አርፌአለሁ በውኃ ዳር እንደአለች ተክል ፍሬያማ ሆኛለሁ የረገጥኩት ምድር በአንተ ሲገዛ አይቻለሁ ስምህን ጠርቼ ጌታ መቼ አስነካለሁ ያየሁትን የሰማሁትን (የሰማሁትን) እናገራለሁ ያረፍኩበትን (ያረፍኩበትን) (2x) ሞተና በሶስተኛው ቀን ተነሳና ሞተና በሶስተኛው ቀን ተነሳና ነፃ አደረገኝ ዕዳዬን ከፈለና