ዓይኖቼን ወደተራሮች ባቀና ረዳቴ ይመጣል ብዬ ደጅን ብጠና ግን ተራራዎች መልስን ሰጡኝ በዝምታቸው ሚስጥሩ ገባኝ እነርሱም እርዳታ እንደሚያሻቸው ከታራራውም ላይ አሻቅቤ ሳይ በላይ በሠማይ ረድኤቴ መጣ እይተራመደ በደመናት ላይ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማንም እንደሌለ ይህንን ስላየሁ የዘለዓለም አምላክ መኖሪያዬ አድርጌዋለሁ (2x) እንደተፈታች ሚዳቋ እንደተፈታች እንደተፈታች እምቦሳ እንደተፈታች ልውጣ ላይ ልውረድ ታች ነፍሴ ሃሴት ስላረገች ቧረቀች ፈነደቀች ነፍሴ ሃሴት ስላረገች (2x) እስቲ ክበር በሉት ክበር እስቲ ንገሥ በሉት ንገሥ ጌታን ክበር በሉት ክበር ጌታን ንገሥ በሉት ንገሥ እጅግ ደስ ይለኛል ሥሙ ሲወደስ ይንገሥ ይንገሥ ይንገሥ (2x) ይንገሥ ይንገሥ ይንገሥ ክበር ክበር ክበር ንገሥ ንገሥ ንገሥ ይክበር ይክበር ይክበር ይንገሥ ይንገሥ ይንገሥ በእኔና በሞት መካከል አንድ እርምጃ ቀርቶ እርሷንም ተራምዶ ውጦ ሊያስቀረኝ እጅጉን ጓግቶ በጠላትም ሰፈር በቃ ሽንፈቴ ተረጋገጠ ግን ረዳቴ መጣ በቅጽበት ነገሩ ተገለበጠ ሊሰለጥንብኝ ባለው ቀን ጠላቴ ሰለጠንኩበት ለእኔ በቆፈረው ጉድጓድ እርሱ ተቀበረበት ድል አድራጊው ጌታ ድል እያደረገ በሰልፉ መሃል በምሥጋና ነዶ በምርኮ ብዛት ያዘምረኛል/ያዘልለኛል (2x) እንደተፈታች ሚዳቋ እንደተፈታች እንደተፈታች እምቦሳ እንደተፈታች ልውጣ ላይ ልውረድ ታች ነፍሴ ሃሴት ስላረገች ቧረቀች ፈነደቀች ነፍሴ ሃሴት ስላረገች (2x) እስቲ ክበር በሉት ክበር እስቲ ንገሥ በሉት ንገሥ ጌታን ክበር በሉት ክበር ጌታን ንገሥ በሉት ንገሥ እጅግ ደስ ይለኛል ሥሙ ሲወደስ ይንገሥ ይንገሥ ይንገሥ (2x) ይንገሥ ይንገሥ ይንገሥ (3x) ንገሥ ንገሥ ንገሥ ይክበር ይክበር ይክበር ይንገሥ ይንገሥ ይንገሥ