እግዚአብሔር ባይራራልኝ ልጁን ልኮ ባይታደገኝ የጠላት ሴራ ወጥመድ ዘርግቶብኝ በሙታን ሰፈር እዛው ላይ በቀረሁኝ ግን አልተሳካም አልሆነለትም ነፍሴ ከቶ አላገኛትም በክርስቶስ በተሰራው ስራ አመለጠች እንደወፍ በራ አመለጠች/4 ነፍሴ እንደወፍ ከአዳኞች ወጥመድ አመለጠች በርራ በርራ እንደ ወፍ በርራ /2 አመለጠች በርራ /2 በክርስቶስ ስራ አመለጠች በርራ በመስቀል ላይ ስራ አመለጠች በርራ አዳኙ በስውር ወጥመድ አስቀመጠ ከአሁን አሁን ያዘልኝ ሲል አይኑ እንዳፈጠጠ አዳኜ ሲመጣ ወጥመዱን ሲረግጠው ነፍሴን አስመልጦ ቀንበሩን ሰባበረው /4 እንዲህን ነው ያመለጠችው ነፍሴ/2 እንደወፍ አመለጠች ነፍሴ /2 በረረች አመለጠች ነፍሴ /2 በአዳኝዋ በኢየሱሴ/4 በኢየሱሴ ሞትና ሲኦል አንድ ላይ ተስማምተው ዘላለሜን ሊያደርጉት በድቅድቅ ጨለማው የትንሳኤው ጉልበት ሞትን ራሱን ገድሎት መውጊያውን ሰባብሮ ነፍሴ አስመለጣት/4 እንዲህን ነው ያመለጠችው ነፍሴ/2 እንደወፍ አመለጠች ነፍሴ /2 በረረች አመለጠች ነፍሴ /2 በአዳኝዋ በኢየሱሴ/4 በኢየሱሴ