ሰማያትን ቀና ብዬ እንደማይ ሳየውም ሩቅ እንደሆነ አምላኬ እንደእዛ አላይህም እግዚአብሔር እንደእዛ አላርቅህም ቅርብ ነህ ለእኔ አለህ አጠገቤ (4x) ሰማይ ሰፋህ አልለው ትልቅ ነህ ጌታዬ ግን መረጥክ ልትገባ ልትቆይ ከልቤ የታሰበ ኧረ ነው ለአንተ የተዘጋጀ ስለዚህ አውቃለሁ አጠገቤ እንዳለህ አዝ:- ቅርቤ ነህ ከጐኔ ነህ (2x) ይሰማኛል ህልውናህ (2x) የጠየኳቸው ጥያቄዎች ሁሉ መልስን ብትሰጣቸው ወይም ቢዘገዩ እነሱንም አይቼ ቅርቤ አላልኩህም እስከ ፍጻሜ ከእኔ ጋር ነህ አመንኩት ቃልህን አዝ:- ቅርቤ ነህ ከጐኔ ነህ (2x) ይሰማኛል ህልውናህ (2x)