የፈርዖን ገንዘብ ያልማረከው ጀግና ዓይኑ ያልደከመ ያላለቀ ገና ድል ለማድረግ ወጣ በጦርነት ሲቃ በጀርባው አንግቦ የአምላኩን ጦር ዕቃ (2x) የወይኒው አስራት የግርፋት ብዛት አልቻለው ሊያበርደው የፍቅሩን ትኩሳት ፎከረ ያ ጐበዝ ሊጥል ሊገረስስ ጠምዶ በቀኝ እጁ የቃሉን መትረየስ (2x) ገና ዓይኑ ፍጦ ትኩር ብሎ እያየ የጠላትን ምሽግ ቅጥሩን አጋዬ የአርያም እሳት በኃይል ጐብኝቶታል እባቡና ጊንጡን ከእግሩ ስር ረግጦታል (2x) በድካም በረታ ጅማቱ ጠንክሯል አንገብግቦት ፍቅሩ ወኔው ተቀስቅሷል በጀርባው መተልተል ጌታን አከበረ የሞትንም ባሕር በእምነት ተሻገረ (2x)