በአምላክ አምሳል ተፈጥሬ በጐ ለማድረግ በፊቱ ስኖር ሳለሁ ኃጥያቴ አድርጐኝ ነበር ከንቱ ክቡር ሆኜ ሳለሁ አምላኬን ረስቼ እንደሚጠፉ እንስሶች መሰልኩ እኔ ሳልፈልገው ጌታ ሊፈልገኝ ከላይ መጥቶ ከእርኩሰት ውስጥ ነጥቆ አወጣኝ በዓለም ላይ ተንከራቶ ሸክሜን ወሰደልኝ በሥጋዬ ሞተልኝ የማይቆጠረውን በደሌን ፋቀልኝ መድኃኒቴ ነው ኢየሱሴ ጌታዬና አምላኬ ስለ መልካሙ ውለታው ላመስግነው ተንበርክኬ ምህረቱ ብዙ ነው ማዳኑ ግሩም ነው ለአምላካዊ ፍቅሩ መጨረሻ የለው በሞት ጥላ ውስጥ እያለሁ በድቅድቅ ጨለማ ኢየሱስ ብርሃኔ መጥቶ አዳነኝ መሀሪ ነውና ለፍርድ የተመደብኩ ለሲዖል የታጨሁ የቁጣ ልጅ ስሆን ከፍጥረቴ ቅጣቴን ውስዶ ያ ረድኤቴ (2x)