የሙታን ባልንጀራ ኃጢአተኛ ሳለሁ ጌታን በማመኔ ከክፋት ድኛለሁ ግን ሕይወቴን እንድክድ አሁን ብከተልም ኢየሱሴን ክጄ ግኡዝ አላመልክም አዝ፦ እምቢ አሻፈረኝ ለምስሉ አልሰግድም ለሰው እጅ ሥራ አልንበረከክም ከናቡከደናጾር የቁጣ ነበልባል የማመልከው ጌታዬ በእርግጥ ያድነኛል እቶኑ ይታየኛል ግለቱ ይሰማኛል ፈርቼ አልጠላውም አንስቶ ያጠራኛል ለሰማያዊው መንግሥት ብቁ ያደርገኛል ሰው እንደሚያስበው መቼ ይጐዳኛል አዝ፦ እምቢ አሻፈረኝ ለምስሉ አልሰግድም ለሰው እጅ ሥራ አልንበረከክም ከናቡከደናጾር የቁጣ ነበልባል የማመልከው ጌታዬ በእርግጥ ያድነኛል በእሳት ውስጥ ያሉትን ጭሱ ሳይነካቸው አስረው የጣሏቸው ወላፈን ፈጃቸው እንደዚህ የሚሰራ ኃያል ጌታ ካለኝ ሰባት እጥፍ ያንድድ እኔ ምን ቸገረኝ አዝ፦ እምቢ አሻፈረኝ ለምስሉ አልሰግድም ለሰው እጅ ሥራ አልንበረከክም ከናቡከደናጾር የቁጣ ነበልባል የማመልከው ጌታዬ በእርግጥ ያድነኛል እምቢ (3x)