አንድን ነገር ሽቼ ደጅ ጠናለሁኝ ፈቃድህ ከሆነ በዓይንህ ተመልከተኝ ያቺን ብሩክ እጅህን ዘርጋብኝ አዝ፦ እንባዬን አይተህ ጌታ ለቅሶዬን ሰምተህ ጌታ መሻቴን ስጠኝና ኢየሱስ ላመስግንህ (2x) አንተን ተስፋ አድርጌ በቃልህ ፀንቼ መልሴን አጠብቃለሁ በተመስጦ ሆኜ ታማኝነትህን ተማምኜ አዝ፦ እንባዬን አይተህ ጌታ ለቅሶዬን ሰምተህ ጌታ መሻቴን ስጠኝና ኢየሱስ ላመስግንህ (2x) በጐ ስጦታና ፍፁም በረከት ሁሉ ከብርሃናት አባት ከላይ ይወርዳሉ ከዙፋንህ ይንቆረቆራሉ አዝ፦ እንባዬን አይተህ ጌታ ለቅሶዬን ሰምተህ ጌታ መሻቴን ስጠኝና ኢየሱስ ላመስግንህ (2x) መራራነቴ ያብቃ እሾህነቴም ያብቃ መፈራረሴም ያብቃ በአንተ ፀጋ ልገንባ ጐስቋላነቴን ጌታ ሆይ እንካ አዝ፦ እንባዬን አይተህ ጌታ ለቅሶዬን ሰምተህ ጌታ መሻቴን ስጠኝና ኢየሱስ ላመስግንህ (2x)