ስርዓትህን ንቀን ቃልህን አቃለን መንፈስህ ሲወቅሰን ሁሌ እንሰማለን ሥጋ ብቻ ሆነን በአመፅ ተውጠናል እራስን መመርመር ፍፅም አቅቶናል አዝ፦ በከፍታ ስፍራ በሰማይ ያለኸው ምንም አይሳንህ ሁሉን ቻይ የሆንከው ልብን ኩላሊትን የምትመረምረው ጌታ ሆይ ጓዳችንን አፅዳ አጥበህ አስተካክለው ያኔ ስትልከን ጦርእቃህን ሰጥተህ ኃይል በኃይል አድርገህ ሞገስ አከናንበህ ከጦር ሜዳው ወጥተን ድልን ሰጥተኸናል ዛሬ ግን ወዮልን ጠላት ስቆብናል አዝ፦ በከፍታ ስፍራ በሰማይ ያለኸው ምንም አይሳንህ ሁሉን ቻይ የሆንከው ልብን ኩላሊትን የምትመረምረው ጌታ ሆይ ጓዳችንን አፅዳ አጥበህ አስተካክለው እንደ ቀድሞ መስሎን እንዋጋ ብንል በብዙ ለማጥመድ መረቡን ብንጥል ከንቱ ልፋት እንጂ ምርኮ ከየት ይምጣ ግራ ተጋብተናል በከንቱ እሩጫ አዝ፦ በከፍታ ስፍራ በሰማይ ያለኸው ምንም አይሳንህ ሁሉን ቻይ የሆንከው ልብን ኩላሊትን የምትመረምረው ጌታ ሆይ ጓዳችንን አፅዳ አጥበህ አስተካክለው አሁን ተረድተናል ኃጢአት አድርገናል በትዕቢት ፍላጻ አስለቅሰሃል በእርማችን ምክንያት ፊትህ ከብዶብናል ጌት ሆይ ታረቀን ማረን ብለንሃል አዝ፦ በከፍታ ስፍራ በሰማይ ያለኸው ምንም አይሳንህ ሁሉን ቻይ የሆንከው ልብን ኩላሊትን የምትመረምረው ጌታ ሆይ ጓዳችንን አፅዳ አጥበህ አስተካክለው