ማሰሮው ሲሰበር ድብቁ ብርሃን ይወጣል ስንዴው ሲበሰብስ ቡቃያው ብዙ ያፈራል ጌታዬ አምላኬ የተሰበረ ልብ ያሻኛል ድምፅህን እንድሰማ የተግሳጽ ይሁን ወይም የምክር በድንግዝግዝ ጊዜ ወድቄ እንዳልሰበር ጌታዬ አምላኬ የተከፈተ ጆሮ ያሻኛል አንተን ለመመልከት ሁልጊዜ በፊቴ ስትሄድ ወደ ቀጠሮአችን ቦታ በብርሃንህ እንድራመድ ጌታዬ አምላኬ ጤንነት ያለው ዓይን ያሻኛል ሰላምን ለማውራት የምሥራች ይዤ እንድሮጥ ፅድቅን ለተጠሙ ምንጩን እነሆ ለማለት ጌታዬ አምላኬ የሚራመዱ እግሮች ያሹኛል