ጌታ ለኔ ያድረከው ልቆጥረው አልችልም ወለታህ ብዙ ነው ኢየሱስ ስለወደድ እወድሃለሁኝ አከብረሃለሁኝ ተመስገን እያልኩኝ ሳላውቅህ አውቀኸኝ ሳልወድህ ወድኸኝ በምረትህ ከበህ ቤትህ አኖርከኝ ከነፍሴ ምሥጋና ለአንተ እሰዋለሁ ምህረት ቸርነትህን እናገራለሁ በዘመኔ ሁሉ አንተን አከብራለሁ አልታዘዝም ስል በደሌን ታግሰህ በፍቅርህ ገመድ ወዳንተ መልሰህ ስወድቅ አንስተኸኝ ስዝልም ደግፈህ እዚህ አደረሰከኝ ጌታ ምን ልበልህ የሚመስልህ የለም ኢየሱስ ፍቅር ነህ ለዘለዓለምም የማትተወኝ በዘለዓለም ፍቅርህም የወደድከኝ ጌታ ኢየሱሴ የነፍሴ እረኛ ወዳጄ ነህ ለኔ የማትተኛ የማትለየኝ ስነቃም ስተኛ አትለዋውጥም ሁልጌዜ ታማኝ ነህ ፈጥነህ ትደርሳለህ ስምህን ለሚጠሩህ ኢየሱስ አምባዬ ለኔ መጠጊያዬ ዞሮ መግቢያዬ ነህ መሸሸጊያዬ ከመከራ ሁሉ መዳኛዬ