ውለታው አምላኬ ለኔ ያደረገው አያልቅም ባወራው ከእምሮ በላይ ነው ተመስገን ልበለው በምድር ላለው ለእንዳዱ ሰው ግድ የተሰኘው ራሱን ለዓለም ቤዛ አድርጐ እንዲሁ የሰጠው ለጠሉትና ላልተቀበሉት ሆኖ መስቀል ላይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቀር በል አባት ሆይ ያለው ይሄ ጌታ ምን ዓይነት ፍቅር ነው ምንስ ዓይነት ቋንቋ ይችላል ሊገልጸው በምድር ካሉ ከተዋረዱ ከድሆች በላይ ኢየሱስ ስለእኛ ቤዛ ሆነልን መጥቶ ከሰማይ የሁላችንን በደልና ኃጢአት ተሸከመልን እዳችንን እርሱ ከፍለ ነጻም አወጣን በፍፁም ልባችን ጌታን ብንወደው አይገባውም ወይ ለእኛ ላደረገው መች በዚህ ብቻ በዚህ አበቃ የኢየሱስ ፍቅር ከእርሱ ጋራ ወራስህ አረገን አብሮን የምኖር የእርሱ የሆነውን አንዳችም ሳይቀር ለእኛ ሰጠው ባርኮቱን ሁሉ ምንም ሳይሰስት ለእኛ አፈሰሰው ታዲያ ለዚህ ጌታ ለእርሱ ብኖርለት ይገባዋል እንጂ መች በዛበት ይህንን ውለታ የዋልልን ኢየሱስ ይመጣል በዚህች ምድር ላይ ናፍቀን እንቀርም መጥቶ ይወስደናል ወዳችንን በዓይናችን እናዋለን ወድቀን ከእግሩ ስር እንወድሃለን እንለዋለን ከተስፋ ሁሉ በላይ የተባረከው ተስፋችን ጌታ ኢየሱስ ነው ስናየው ባይናችን