የሚያስፈልገኝን እርሱ ያውቃል የሰማይ አባቴ ለኔ ያስባል እጆቼን ወደ እርሱ ዘረጋለሁ በዘለዓለም አምላክ እታመናለሁ የሚያስጨንቀን በእርሱ ጥዬ እታመናለሁኝ በጌታዬ ጽድቁና መንግሥቱን እሻለሁኝ ክብሩን እያየሁኝ እጠግባለሁኝ ላመልከው ብቻ ነው የፈጠረኝ ከእርሱ ሌላ ምንም ላይገዛኝ እያሞጋገስኩኝ ታላቅ ስሙን አመልከዋለሁኝ እግዚአብሔርን የጠራኝ የለየኝ የቀደሰኝ ለእርሱ ካህን ልሆን ነው የቀባኝ እርሱ ያደረገኝ እሆናለሁ የኣምላኬን በጐነት አወራለሁ መልካሙን ስራውን የጀመረው የጠራኝ እግዚአብሔር ታማኝ ነው እስከ ክርስቶስ ቀን ሊፈጽመው ይችላል አምላኬ ታማኝ ነው