የዓለም ምናምንቴ አይስበኝም ከቶ አያምረኝም የሚያብረቀርቀው አይገዛኝም ከቶ አያታለኝም በሚያልፈው በሚጠፋው አልማልልም ከቶ አልጎመጅም ሀሳቤ ተወርሷል ባንተ በኢየሱስ ነብሴን የሚያረካት ፍቅርህ ነው በፊትህ መፍሰስ እወድሃለው ከውስጤ ከአንጀቴ አንተ ብቻ እኮ ነህ የሞላኸው ቤቴ ብዬ ብዬ አልጥግብ ስላንተ ባወራ የህይወት ውሃ ነህ የህይወት እንጀራ እራብሃለው እራብሃለው ጌታ መድኃኒቴ አንተን እሻለው እጠማሃለው እጠማሃለው ኢየሱስ መድኃኒቴ አንተን እሻለው የፀዳልህ ብርሃን ሚናፈቀው ክብርህ የልቤ ተማጥኖ እንዳየው ያን ፊትህ ምጠይቅህ የለ ከእጅህ እንድቀበል ግን እንዲያው ዝም ብዬ ከእግርህ ቁጭ ልበል ገና በማለዳ ወደ አንተ እሮጣለው የመንፈስህ እሳት ህይወቴን ያግለው ልማርህ እሻለው እንዳውቅህ አጥብቄ ከህልውናህ ጋር ልኑር ተጣብቄ ፈልግሃለው እስካገኝህ ድረስ እጣደፋለው እጠማሃለው ጌታ መድኃኒቴ አንተን እሻለው ክብሬ ነህ አዶናይ ቀኔን የምታፈካ የምትሰጠው ደስታ በምንም ማይተካ አብሮነትህ እኮ ነው ህይወቴን ያጣመ ዛሬም ልቤ አንተን አንተን ብቻ አለመ ገና በማለዳ ወደ አንተ እሮጣለው የመንፈስህ እሳት ህይወቴን ያንድደው ልማርህ እሻለው እንዳውቅህ አጥብቄ ከህልውናህ ጋር ልኑር ተጣብቄ እወድሃለው ከውስጤ ከአንጀቴ አንተ ብቻ እኮ ነህ የሞላኸው ቤቴ ብዬ ብዬ አልጥግብ ስላንተ ባወራ የህይወት ውሃ ነህ የህይወት እንጀራ እራብሃለው እራብሃለው ጌታ መድኃኒቴ አንተን እሻለው እጠማሃለው እጠማሃለው ኢየሱስ መድኃኒቴ አንተን እሻለሁ