ተሰሚ ነህ በሰማይ በምድር ጉልበት ሁሉ ሚንበረከክልህ የፈጠርከን እንሰግድልሃለን ሞገስህን ክብርህን እያየን ይሹሩን ሆይ በሰማያት ላይ ለእረድኤትህ በደመናት ላይ እንደሚሄድ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማንም የለም ኧረ እንደርሱ ያለ ቢፈለግም የለም (2x) ዘመንህ ዘላለም ከቶ አታረጅም አምሳያ የለህም መቼም አትተካም አዬዬ መቼም አትተካም ፊትህ እንደ ፀሐይ በሀይል የሚያበራ ከዋክብት ጨረቃን ደመናን የሰራህ አዬዬ ፀሐይንየሰራህ የአማልክቱ አምላካቸው ነህ የፍጥረት ገዢ የዓለማት ንጉሥ ነህ ወሰን የሌለህ ስራህ እረቂቅ የማትታወቅ የሆንህ እጅግ ታላቅ እንዳንተ ያለ ቢፈለግም የለም ኧረ እንዳንተ ያለ ታላቅ አምላክ የለም እንዳንተ ያለ ቢፈለግም የለም ኧረ እንዳንተ ያለ አይኖርም ዘላለም የዓለም ሁሉ መሪ ብርቱ ነህ ሀይለኛ ከሁሉ ቀዳሚ የሌለህ ፊተኛ አዬዬ የሌለህ ፊተኛ ይሁን ባልከው ቃልህ ሁሉ ተፈጠረ እቅድህ ግሩም ነው ስራህም ያማረ አዬዬ ስራህም ያማረ የአማልክቱ አምላካቸው ነህ የፍጥረት ገዢ የዓለማት ንጉሥ ነህ ወሰን የሌለህ ስራህ እረቂቅ የማትታወቅ የሆንህ እጅግ ታላቅ እንዳንተ ያለ ቢፈለግም የለም ኧረ እንዳንተ ያለ ታላቅ አምላክ የለም እንዳንተ ያለ ቢፈለግም የለም ኧረ እንዳንተ ያለ አይኖርም ዘላለም (2x)