አለማመን ሲታመን መናኝ ተጓዥ ሲጠፋ ዓለም ጨርቋን ስትጥል ሁሉ ለባዶ ሲለፋ እውቀት ትዕቢት ሲሆን ጥበብ መጀመሪያው ሲገፋ ሞኝ መባልን ምረጥ ተያይዘህ እንዳትጠፋ እግዜሩ አለ በል በኑሮ ስብከቱማ አዝሏል የሁሉን ጆሮ እውነት የመኖር ክብደት ከሌለው ንግግርማ ቀላል ነው ያላዩት ብርሃን ይታይህ ቀንህ ለአንተ ይታዘዝ በቀደዱልህ እንዳትሾልክ አጥሩን ገንጥለህ እለፍ ፍቅርን መኖር ከሞከርህ እውነትን ዕድል ከሰጠኸው የለም ያሉትን ያዩታል ወኪል መሆን ይሄ ነው እግዜሩ አለ በል በኑሮ ስብከቱማ አዝሏል የሁሉን ጆሮ እውነት የመኖር ክብደት ከሌለው ንግግርማ ቀላል ነው ልለይ ከከንቱ ማይጠቅም ሁካታ ከሚያደነዝዝ አልፍቶ የሚያሳጣ እርካታ የአምልኮን መልክ ይዤ አልቅር በመንፈስ ደንዝዤ ጩኸት ያለበትን ስከተል ጎድዬ አልቅር ከቁም ነገር እውነት ምንድነው ርምጃዬን ካልወሰነ ሃሳቤን ካላረቀ በስልጣኑ ካልበየነ እንዲሁ ለመልክ ስምህን ከምጮኸው የእውነት ልወቅህና አለመታዘዜን ጣለው ስበረው ከልብ አውቄህ ከልብህ መኖር ልጀምር ፍጥረት ይህንን አይቶ ፍቅርህን አብሮኝ ይዘምር ከንቱነትን ሳሳድድ ዘመኔ ከሚያልቅብኝ ዝናውም ዕውቅናውም መድረኩም ሁሉም ይሂድ ይቅርብኝ እግዜሩ አለ በል በኑሮ ስብከቱማ አዝሏል የሁሉን ጆሮ እውነት የመኖር ክብደት ከሌለው ንግግርማ ቀላል ነው