የደመቀ ብርሃን ለብሰህ እንደሸማ እግዚአብሔር ኃያል ታላቅ ባለግርማ አምላካችን ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ ለታላቅነትህ መላዕክት ይሰግዳሉ እኔም ከእነርሱ ጋር አብሬ ገና አልጠገብኩም ዘምሬ ሳመልክህ ነው ደስ የሚለኝ ሳደንቅህ ነው ደስ የሚለኝ ሳላመልክህ እንዴት እውላለሁ ሳላደንቅህ እንዴት ብዬ አድራለሁ ሳመልክህ ነው እኔ ደስ የሚለኝ ሳደንቅህ ነው እኔ ደስ የሚለኝ አንተ የምትመለክ ነህ አንተ የምትደነቅ ነህ*2 የወንዝ የፏፏቴው የተራሮች ግርማ ሥራህን ያውጃሉ በሚጣፍጥ ዜማ ፍጥረታት ሲያከብሩህ ቃላቸው ተሰማ እኔም ከእነርሱ ጋር አብሬ ገና አልጠገብኩም ዘምሬ ሳመልክህነው ደስ የሚለኝ ሳደንቅህ ነው ደስ የሚለኝ *2 ተመለክ በዙፋንህ ላይ በላይ በሰማይ ተመለክ ባለህበት በማደሪያህ ላይ ተመለክ የልቤ አምላኬ ሆይ ለዘለዓለም ተመለክ እወድሀለሁኝ ዛሬም ቢሆን ነገም ሳላመልክህ አመልክሃለው *4