ያለ ምህረትህ ማነው የኖረው አንድ ጀምበርስ ማነው የዋለው *2 ፍቅርህና ምህረትህ ተከትለውናል በቤትህ ዘላለም ይኸው ያኖሩናል *2 ምህረትህ ከሕይወት ይሻላል እስከዛሬ ይሄው አኑሮናል አንተን አምላክ እኛን ሕዝብ አድርጎ ያቆራኘን ምህረትህ ነው እኮ ያለ ምህረትህ ቸርነትህን በዐይናችን አይተናል በምህረትህ ከቁጣህ ድነናል ለኃጢአታችን ይቅርታህ መልስ ሆኖ ተሸከምከን ፍቅርህ በእኛ ገንኖ ያለ ምህረትህ ከሞት ግዛት ከድቅድቅ ጨለማ አፈለስከን ወደ ጽድቅ ከተማ በኃጢአታችን ሙታን ሆነን ሳለን ከኢየሱስ ጋር ሕይወትን ሰጠኸን ያለምህረትህ እናወራለን ያንተን በጎነት አምነን በጸጋህ ስለዳንንበት የማይተመን እጅግ የላቀ ጌታ ምህረትህ በእኛ ታወቀ*2