ኤልሻዳይ ብዬ ዘምሬአለሁ ጌታም ነህ ብዬ መስክሬአለሁ አሁን ግን ቃላትን ስላጣሁ ከምለው በላይ ነህ ብያለሁ ከምልህ በላይ ጌታ (3x) ነህ የእኔ ቃላት የማይገልጽህ የሰው ቃላት ከምልህ በላይ ጌታ ነህ እኔን አሳፍሮኝ አያውቅም የማገለግለው ጌታ ያኖረኛል በምድር ላይ ጠላቶቼን እየመታ ለምን ይህን አደረግህ? ብሎ የጠየቀው የለም ሥልጣኑ ከሁሉ በላይ ጉልበቱ ኤልሻዳይ ነው እሠይ (6x) ጌታ ነው በምድር በሰማይ ከሁሉም በላይ ነው ኢየሱስ በምድር በሰማይ ከሁሉም በላይ ስለ በደሌ ዝቅ ብሎ መስቀል ተሸክም ያየው ሰው የሰማይ የምድር ጌታ ነው ብሎ ማን ይገምተው? ቢሆንም ተነሥቶ ጌታ በዓብ ቀኝ ተቀምጧል በሰማይና በምድር ሁሉን አንበርክኳል ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ አይጠቅምም ብለው የጣሉት የትንሣዔ ጌታ ሆነ የናቁትን አሳፍሮ እጅ አስጭኗቸዋል በመንግሥቱም እያበራ ዘለዓለም ይኖራል