አንተ እኮ ለእኔ ጌታ ነህ አንተ እኮ ለእኔ ልዩ ነህ አንተ እኮ ለእኔ ወዳጄ ነህ ሥሜን በሰማዩ መዝገብ መቀመጫዬን በአብ ቀኝ እረፍትን ለዘለዓለም ለዘመኔም ቁጥር የለም ስሄድ በመላዕክት ታጅቤ እኔም በአምላኬ ታስቤ ሰማያት ደስ እያላቸው እኔ መዳኔ ገርሟቸው በትውልድ ላላገኘሁት በትምህርት በዕውቀት በችሎታ የማያልፍ ክብር አውራሼ ልዩ ነህ ለእኔ የእኔ ጌታ ልዩ ነህ ጌታ ልዩ ነህ ልዩ ነህ ኢየሱስ ለእኔስ ልዩ ነህ ስለጥበቃህ አልሰጋም ተጠብቄ አይቻለሁ ስለማዳንህ ብናገር አለኝ ብዙ አወራለሁ አባትነትህማ ለእኔ ሆኖኝ ጧት ማታ ትዝታ እኖራለሁ ተደስቼ በአንተ በአስደናቂ ጌታ በዘመድ አልታመንም ዛሬ ታይቶ በሚጠወልግ ብሩንም አይቼዋለሁ እንደ ጉድፍ ቆጥሬዋለሁ በምንም የማይገመት ሀብቴ ትምክህቴ ልዩ ኩራቴ የሕይወት ዘመን ምርጫዬ አንተ ነህ ለእኔስ ጌታዬ ማንም ላይገዛኝ ኖራለሁ ሁሉን በአንተ አሸንፌአለሁ የሚገዛኝ በዚህ ዓለም ከአንተ ውጭ ማንም የለም ገንዘብ ሀብት ዕውቀት ንብረት በዚህ ዓለም ነገር መጠመድ አበቃ አከተመለት ከአንተ የተገናኘን ዕለት