በማዘን መተከዝ እግዚአብሔር ይከብር ይመስል ምንድን ነው መርበትበት ሁልጊዜ መቆዘም ጠላት ነው እንጂ በዚያ ደስ ደስ የሚለው ምን ይጨምራል የአምላክን ሃይል መጠርጠር ነው አዝ፦ አላንጐራጉርም አንገቴንም አልደፋም እግዚአብሔር እንቅቶኛል ጊዜዬን አላጠፋም (2x) ምን አሸማቀቀኝ ምን አንገቴን አስደፋኝ ጌታዬ ከእኔ ጋር ሆኖ እያየሁኝ የማልፍበት ሁሉ እንደምናምን ቢመስልም ነጥሬ እወጣለሁ ወደኋላዬ አልልም አዝ፦ አላንጐራጉርም አንገቴንም አልደፋም እግዚአብሔር እንቅቶኛል ጊዜዬን አላጠፋም (2x) የትም ስፍራ ብሆን የሚይዘኝ ምንም የለም እሰራለሁ ስራ አለኝ ገና ያልጀመርኩት ሲያየኝ ጠላቴ ለዐይኑ ባልሞላለትም እግሬ የረገጠበት ሰላም አልሰጠውም አዝ፦ አላንጐራጉርም አንገቴንም አልደፋም እግዚአብሔር እንቅቶኛል ጊዜዬን አላጠፋም (2x) የደከምኩ ስመስለው አሳድደዋለሁ ተኛታለች ብሎ ሲል ህልምን አልማለሁ ዛሬ አዘነች ሲል እዘምራለሁ ከአምላኬ ተጣብቄ ግራ አጋባዋለሁ አዝ፦ አላንጐራጉርም አንገቴንም አልደፋም እግዚአብሔር እንቅቶኛል ጊዜዬን አላጠፋም (2x) ትልቅን ትልቅን ነገርን ሁልጊዜ አስባለሁ አምላኬ ያንኑ ሲያደርግ አየዋለሁ ከፍ ያለውን ከፍ ያለውን ነገርን ሁልጊዜ አስባለሁ አምላኬ ያንኑ ሲያደርግ አየዋለሁ (4x)