ጊዜው እየከፋ ሲሄድ ሰው ምን ያደርጋል ጥፋት ሲበዛ ወዴት ይሸሻል መተማመን ጠፍቶ ጥላቻ ሲበረታ የተለፋበት ሁሉ ድርምስምስ ሲል ቀና ነው የተባለው ቅጡ ሲጠፋ ሰው ግራ ተጋብቶ ጭንግር???ጭምር??? ሲለው ወደማን ነው የሚያየው አዝ፦ እንጸልይ ጸሎት የሚሰማ አምላክ አለ እንጸልይ ሳንታክት እንጸልይ ፍርድን የሚወድድ አምላክ አለ በሰማይ (2x) በድህነት ቀመር ተጠፍሮ ህዝብ በድካም ጅራፍ ሲገረፍ ሞትን እንደጨለማ ምድራችንን ሲከብ አንዱ ከአንዱ ሲጋደል አለቆች አልፈቱም ይህን እንቆቅልሽ ከአዋቂቆችም ምክር አልተገኘም ነገሥታት እነርሱ ተሰወረባቸው ድንግዝግዝ አለ ቀኑ አዝ፦ እንጸልይ ጸሎት የሚሰማ አምላክ አለ እንጸልይ ሳንታክት እንጸልይ ፍርድን የሚወድድ አምላክ አለ በሰማይ (2x) እንጸልይ በስሜ የተጠሩ ህዝቤ ራሳቸውን አዋርደው ቢጸልዩ ከሰማይ ሆኜ እሰማለሁ ምድራቸውን እፈውሳለሁ ብሏል ጌታ (2x) አዝ፦ እንጸልይ ጸሎት የሚሰማ አምላክ አለ እንጸልይ ሳንታክት እንጸልይ ፍርድን የሚወድድ አምላክ አለ በሰማይ (2x) እንጸልይ