የምትሄድበት መንገድ ጨለማ ቢሆንብህም በኃይለኛ ውሃ ውስጥ ሳትፈልግ ብታልፍም ከአንተ ጋራ ያለው ከሁሉ በላይ ነው መንገድ አዘጋጅቶ መውጫ ሚያበጅ ነው (ሃሌሉያ) አዝ፦ ተስፋ ቆርጦ (ተስፋ ቆርጦ) ለሚያዘግም (ለሚያዘግም) ለሚሄደው በጨለማ አምላክ አለ (አምላክ አለ) መሪ አለ (መሪ አለ)ጩኸትህን ሁሉ የሚሰማ ተስፋ አትቁረጥ (ተስፋ አትቁረጥ) ወንድሜ ሆይ (ወንድሜ ሆይ) ጌታ ኢየሱስ ይወድሃል ወደ እቅፉ (ወደ እቅፉ) ጉያ ግባ (ጉያ ግባ) ኧረፍቱ ይመራሃል ተራራው ከፊት ሆኖ የሩቁን ቢጋርድብሽ ተስፋሽ ሁሉ ጨልሞ የተተውሽ ሲመስልሽ ታምነሽ ጸንተሽ ቁሚ (ጸንተሽ ቁሚ) በሰራዊት ጌታ ሁሉን በሚያሸንፍ (በሚያሸንፍ) ሁሉን በሚረታ (ሃሌሉያ) አዝ፦ ተስፋ ቆርጦ (ተስፋ ቆርጦ) ለሚያዘግም (ለሚያዘግም) ለሚሄደው በጨለማ አምላክ አለ (አምላክ አለ) መሪ አለ (መሪ አለ) ጩኸትሽህን ሁሉ የሚሰማ ተስፋ አትቁረጥ(ተስፋ አትቁረጥ) ወንድሜ ሆይ (እህቴ ሆይ) ጌታ ኢየሱስ ይወድሻል ወደ እቅፉ (ወደ እቅፉ) ጉያ ግባ (ጉያ ግባ) ኧረፍቱ ይመራሻል እርሱ እግዚአብሔር ነው በፍቅሩ እውነተኛ ለመንጋው የሚራራ ታማኝ የሆነ ኧረኛ ከልብ ለሚጠሩት ፈጥኖ የሚደርስ ለጥያቄ ሁሉ መልስ ነው ኢየሱስ (ሃሌሉያ)