አሻግሬ አያለሁ ያንተን መልካምነት ከቶ አልገምትህም አሁን ባለሁበት ታሪክ የምትለውጥ ሁሉንም የምትቀይር እኔ የማመልክህ ድንቅነህ እግዚአብሔር አዝ፦ ለእኔ የምታስበው በጐና ያማረ ነው (3x) አመሰግንሃለሁ (3x) አመሰግንሃለሁ (3x) የተገለጠውን ነገር ጸራለህ በላይ ተሰውረህ ድንቅን ታደርጋለህ ተዐምራትህ ብዙ እጅግ የበዛ ነው ጌታ አሰራርህ ከሁሉም ልዩ ነው አዝ፦ ለእኔ የምታስበው በጐና ያማረ ነው (3x) አመሰግንሃለሁ (3x) አመሰግንሃለሁ (3x) ከሁኔታዎች በላይ ቃልህን አምናለሁ ሚሰማኝን ሳይሆን የሩቁን አያለሁ ከእንግዲህ ታምኜ በእምነት እኖራለሁ የተናገርከኝንም እንዳገኝ አውቃለሁ (2x) ኃይልህ ብዙ ሳለ ጠላቶች ቢዋሹም አንተ ግን አንተ ነህ ከቶ አትለወጥም መልካምነትን በማድረግ ደስ ይለሃልና አቤቱ የእኔ ጌታ ይሁን ለአንተ ምሥጋና አዝ፦ ለእኔ የምታስበው በጐና ያማረ ነው (3x) አመሰግንሃለሁ (3x) አመሰግንሃለሁ (3x)