በለቅሶ የዘራሁትን በደስታ አጨድኩት ምርኮዬም ተመልሷል በብዙ በረከት ሚስጢሩ አንድ ነው የማምለጫው መንገድ እግዚአብሔር ድንቅ ነህ ግሩም ነህ ማለት ጌታን ላመስግን ባልሆነው በሆነው በዚያ ሠፈር ብቻ ድልን ተቀዳጀሁ ዛሬ እንደ ትላንት መች አለቅሳለሁ ቁልፉን አስይዘኸኝ የምሥጋናን በትር ጠላቴን ረግጬ አንበረክከዋለሁ በፎከረብኝ ላይ ቆሜ እፎክራለሁ ከሚውጠው ጉድጓድ ከሚያሰጥም ማጥ አውጥቶ አቆመኝ እግሮቼን በዓለት መች ተንሸራተትኩኝ በቃሉ ላይ ቆሜ ድልን ተቀዳጀሁ እንዲያውም በአምላኬ ልግለጥ ልግለጥ ምርጡን የጦር መሳሪያዬን ላንበልብለው ዛሬ ጠላቴም ይሸበር የመንፈስን ሠይፍ አጥብቄ ይዣለሁ ጠላቴን ቆርጬ አጋድመዋለሁ ከደም ከሥጋ ጋር ውጊያን አቁሜያለሁ ነገሩ ገብቶኛል አሁን ነቅቻለሁ ዘመን መጣ መጣ የዜማ ወራት ከሁሉም ይሰብሰብ ይግባ ለአምላክ ከንፈሮቼን ልክፈት አንደበቴም ያውራው ቅኔም ይደርደር ከዝማሬ ጋራ ታማኝነትህን ማዳንህን ልንገር ሌላ ሰው አልሻም እኔው ነኝ ምስክር ቀረ መሸማቀቅ አቀርቅሮ መሄድ ቀንበር ተሰበረ ቀንቅ ብዬ እንድሄድ