እየመሽ ነጋ እየነጋም መሽ ዛሬም ጉስቁልና ከምድሪቱ እልሸሸ የነገዋ ፀሐይ ሙቀት ይዛ ትምጣ የሃገር ልጅ በርዶታል ድሪቶም ስላጣ ከትናንት ዛሬ ይሻል ይሆን ብለን የበጐ ቀን ያለህ አልመጣም ጠብቀን በደረቀ ላንቃ ውኃ እያረረበት አየን በአደባባይ ፍጥረት ሲንከራተት ገና ነው ምህረቱ አልወረደም የሃገሬ ንዳድ ዛሬም አልበረደም ገና ነው ቁጣው መቸ ሰከነ በሽታና ርሃብ በሃደሬ ገነነ በረሃብ ጉስቁልና በጥማት ተቃጥሎ በብርድ ተጠብሶ በፀሐይ ከሳስሎ ኑሮ እንደሬት መሮት ለሞቱ የሚጐመጅ በጐዳናው ከፈፍ ተዘርግቷል እድጅ እየመሽ ነጋ እየነጋም መሽ ዛሬም ጉስቁልና ከምድሪቱ እልሸሸ የነገዋ ፀሐይ ሙቀት ይዛ ትምጣ የሃገር ልጅ በርዶታል ድሪቶም ስላጣ ማረን ጌታችን ፈጽመህ አትቅጣን ጠበልክን እርጨን ጠምቶናል አጠጣን ታማሚው ይፈወስ የራበው ሰው ይጥገብ የፍርድ አዋጅ በቅቶ ምህረቱ ይነበብ ክራራይሶ (2x) እግዚኦ ማሃረነ ክርስቶስ (2x)