ድሮ ገና ከማህፀን ሳለሁ በእናቴ ሆድ በሥም ጠርተህ የለየኸኝ ክፉን ደጉን ሳላውቅ የአንተ ክብር መገለጫ እንድሆን በቤትህ ከነኃጢአቴ የመረጥከኝ ለአንተ እንድኖርልህ በሰጠኸኝ መንገድ ስሄድ ባሰብክልኝ ስፍራ እንዳልገኝ ሳሳዝንህ ቸል ብዬ ሳልሰራ ዛሬ በቀን ለምንሃለሁ ኃይልህ እንዲረዳኝ በመክሊቴ ብዙ አትርፌ አንተን ደስ እንዳሰኝ አዝ:- ኃይልህ ይርዳኝ ለምናለው እንድትረዳኝም አምናለሁ መልካም ነገር ያደረኩኝ መስሎኝ ሳሳዝንህ እንዳልገኝ ስመላለስ በዚህች ምድር ሳገለግል አንተን ለማልኖረውን አውርቼ የተጣልኩ እንዳልሆን እንዳታልፈኝ እፈራለሁ በምትመጣበት ቀን ሕይወቴማ አንተን ያክብድህ አፌ ብቻ ሳይሆን ክብርህን አሳየኝ የአንተን ማንነት ቅዱሱን መንፈስህን ሚመራኝ ወደ እውነት እኔ ደካማና ኃጢአተኛ ሰው ነኝ ሃይልህ ግን ከረዳኝ ከእግሬ እቆማለሁ አዝ:- ኃይልህ ይርዳኝ ለምናለው እንድትረዳኝም አምናለሁ መልካም ነገር ያደረኩኝ መስሎኝ ሳሳዝንህ እንዳልገኝ ቀድመህ ውጣ በሕይወቴ ልከተልህ ቸሩ አባቴ አንተ ቀድመኀኝ ካልወጣህ እኔ ብሮጥ ምን ላመጣ ለምንሃለሁ ጌታ ለምንሃለሁ ኢየሱስ ኃይልህ ይርዳኝ ጌታ