አቤት ፍቅርህ የሀጥያተኞች ወዳጅ ጓደኛ የጠፋውን ምትፈልግ እረኛ የደሀ አደጎች ሁሉ አባት የምታኖራቸው ባማረ ቤት የመበለቲት ዋና ተሟጋች ጠበቃ ነህ ለተጎዳች ለተጨነቁ ሁሉ ደራሽ የታመሙትን ደግሞ ፈዋሽ አቤት ፍቅርህ ስንቱን ታደገ ከጠፋንበት እየፈለገ ቀና አደረገን ከሸክማችን ጸጋህ ባይረዳን ጠፍተን ነበርን ተማርኬ በፍቅር አመልክሀለሁ ወድቄ ፊትህ በፈቃዴ ደስ እያለኝ ጌታ ኢየሱስ እወድሀለሁኝ ቀኑ ሲመሽ ሰው ሁሉ ሲሄድ የማትቸኩል ለቁጣ ለፍርድ የውስጥ የልብን ሁሉ ተረድተህ እንባን ከአይን ታብሳለህ አሮጌውን ልብስ አውልቀህ ጥለህ የጸጋ ካባን ለእኛ ደርበህ እዳችንንም በመስቀል ከፍለህ ያጸደከን እንዲሁ በፀጋህ አቤት ፍቅርህ ስንቱን ታደገ ከጠፋንበት እያሳደደ ቀና አደረገን ከሸክማችን ጸጋህ ባይረዳን ጠፍተን ነበርን ተማርኬ በፍቅር አመልክሀለሁ ወድቄ ፊትህ በፈቃዴ ደስ እያለኝ ጌታ ኢየሱስ እወድሀለሁኝ እኔም ዋና ምስክር ነኝ አውቃለሁ ከየት እንዳነሳኸኝ በፍቅር እጆችህ እጆቼን እየያዝክ ከስንቱ ጥፋት መለስከኝ