በእርጅና የወለድኩት ልጄ ሞቶብኛል አጥንቱን ሳያስቀር አውሬ በልቶብኛል ወደ ሙታን ስፍራ እያዘንኩ እወርዳለሁ ስለ ዮሴፍ ልጄ ዝምብዬ አለቅሳለሁ ከልጆቼ ሁሉ ይልቅ እወደው ነበር ቀሚስ ገዝቼለት ያጌጠች በህብል አስተዋዩ ልጄ ዮሴፍ ዛሬ ጠፍቷል ከልብሱ በስተቀር ሥጋው ተቦጫጭቋል እነዛ ሁለት ህልሞቹን ስጠብቅ ነበር ልጄን ትልቅ ቦታ እንዳየው ሲከብር ዛሬ የልጄን መርዶ ሰምቼ አዝኛለሁ ሰዎች ቢያጽናኑኝስ እንዴት አጽናናለሁ ይልጆቼን ወሬ አምጣልኝ ብዬ እኔው ነኝ ያዘዝኩት በበረሃ ልጄ እራሴው ነኝ እኔው አውሬ ያስበላሁት የሕይወቱን ጽዋ በአንዴ ያስጨለጥኩት ኧረ ምነው ቢቀርብኝ ባይላክስ ኖሮ ደህና አየው ነበረ ዮሴፍ በእድሜው ከብሮ እናቱም ወንድሙን ስታምጥ ሞታለች ይህንንማ ብታይ ምንስ ትለኛለች እያለ ሲናገር ያዕቆብ በጣም አዝኖ በልጁ ዮሴፍ ሞት እጅግ ተጸጽቶ ልጁን የሚታደግ እግዚአብሔር አለና ዮሴፍ በሕይወት አለ ምስራች ተሰማ አዝ፦ እግዚአብሔር ታድጐታልና ዮሴፍ በሕይወት አለ እንደገና (2x) ሞተ ብለው አረዱት የምስራች አሉ ቃሉ ተፈጸመ ለዮሴፍ ሰገዱ የዮሴፍ ወንድሞች ዮሴፍን ሸጠዋል ግን ጌታ አክብሮት ሻጩን ያሰግዳል አዝ፦ እግዚአብሔር ዮሴፍን ወዶታል በወንድሞቹ ላይ አክብሮታል (2x) ያዕቆብ የእንባው ዘመን ዛሬ አበቃለት የዕድሜውም ፍጻሜ እልልታ ሆነለት የሃያ ብር ባሪያ ዛሬ ጌታ ሆኗል በምድረ ግብጽ ውስጥ ንጉሥ አክብሮታል አዝ፦ እግዚአብሔር ዮሴፍን ወዶታል በምድር ሁሉ ዙሪያ አክብሮታል እግዚአብሔር ታድጐታልና ዮሴፍ በሕይወት አለ እንደገና እግዚአብሔር ታድጐኛልና እኔም በሕይወት አለሁ እንደገና (2x) እግዚአብሔር ታድጐሃልና አንተም በሕይወት አለህ እንደገና እግዚአብሔር ታድጐሻልና አንቺም በሕይወት አለሽ እንደገና እግዚአብሔር ታድጐናልና እኛም በሕይወት አለን እንደገና(2x)