አሻግረኸናል ባሕሩን ከፍለህልናል ውሃውን ፈታችን ሆነህ ስትመራን ማንም አልቻለም ሊያቆመን አረ እንዳንተ ያለ በሰማይ ማን ነው ይፈለግ የበላይ ምድርና ሞላው ያንተ ነው ለሕዝብ ሞገስ የሆንከው ችግራችን የአንተ ችግር ሃዘናችን የአንተ ሀዘን ነበር ለካ የኛ ጌታ ምትክ ሆንከን በኛ ፈንታ እስከ መስቀል ወደድከን ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገርን ተሸከምነው የኛን በደል ፡፡ለዘላለም ኢየሱስ ክበር (2x) ስንደክም ስትበረታ ስንወድቅ ሲታገለን ማን ነው እንዳንተ የቻለን አለሁ ያለ ያልታዬን ወረት ከቶ የማያውቅ ኢየሱስ ብቻ ተባረክ (4x) ሆድ ሲብሰን ይገባሃል ብሶታችን ይሰማሃል ከስትንፋስ ይልቅ ቅርብ ነህ ለእኛ አንተ ታስባለህ ከናት በላይ አሳዳጊ ትዕግሥተኛና አሳላፊ የተጐዳን አስታማሚ ሰው አድርጐ ለክብር ሿሚ ባሕሩ ሲቆም ፊታችን ፈርኦን ሲሮጥ ኋላችን አንተ ነህ ለእኛ የደረስክ ውሃውን ለሁለት የከፈልክ ልባችን በአንተ አረፈ አሳዳጃችን አፈረ መርጦናል ባንተ መደገፍ በምንም ነገር ብናልፍ