የዳዊት የአብርሃም ልጅ ያሉት ነብያት ቀድመው የተረኩት በድንግል በማርያም ያደረ የትውልድ ሐረግ ያስቆጠረ ልደቱ በቤተልሔም በንጉሥ በሄሮድስ ዘመን እረኞች በግርግም ያዩት ኢየሱስ የእኔ መድኃኒት የይሁዳ ምድር አንቺ ቤተልሔም ከይሁዳ ግዛቶች ከቶ አታንሺም እስራኤልን የሚጠብቅ መስፍን ካንቺ ይወጣል ተብሎ እንደተነገረ ኢየሱስ ተወልዷል መልአኩ ወደ ማርያም ገብቶ የሰላም ድምጹን አሰምቶ አምላኬ ፀጋ የሞላብሽ ማርያም ሆይ በይ ደስ ይበልሽ እነሆ ልጅን ትወልጃለሽ ሥሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ በያዕቆብ ቤት ሁሉ ይነግሳል የእግዚአብሔር ልጅ እርሱም ይባላል ነፍሴ ጌታን ትባርከው መንፈሴም አምላኬን ውርደቴን ተመልክቷል የባሪያይቱን ብርቱ የሆነው እርሱ በእኔ ክብሩን ገልጧል ትዕቢተኛን አዋርዶ ትሁቱን አክብሯል ቃል ነበር ቃልም እግዚአብሔር ይህም ቃል በአብ ዘንድ ነበር በእርሱ ሕይወት ትኖራለች ሕይወትም የሰው ብርሃን ነች ከሆነው አንዳች አለእርሱ አልሆነም ሁሉ ሆነ በርሱ ዓለምን ያጸናበት ቃሉ እነሆ ለሚያምኑበት ሁሉ ቃልም ሥጋ ሆነና ፀጋን እውነት ተሞልቶ በእኛ ዘንድ አደረ ክብሩን አየን ጐልቶ በአባቱ እቅፍ ሆኖ አብን የተረከው ቀድሞም የነበረው ቃል ወልድ ኢየሱስ ነው