የእግዚያብሔር ግርማ ክብርና ሞገሱ በፍጥረት ሁሉ ላይ ታይቶ ያወራል ስለእርሱ ፍቅሩ ርህራሄው ቸርነት ምሕረቱ ሁሉም ይዘምራል በዜማ አንደበቱ ሁሉን ቻይነቱ ሳይሆን ገና ሰማይ ሳይሆን ገና ምድር መጀመሪያ እግዚአብሔር ነበር በላይ እና በታች የሚባል ሳይኖር አስቀድሞ እግዚአብሔር ነበር ሳትታይ ጨረቃ ሳትበራ ፀሐይ እግዚአብሔር አምላክ ቀድሞ አልነበረ ወይ ጥዋት እና ማታ ተብሎም ሳይለይ በሥልጣን በክብር እርሱ አልነበር ወይ አዝ፦ በመጀመሪያ እግዚአብሔር በመጀመሪያ በመጀመሪያ የእኔ አምላክ በመጀመሪያ ከሁሉ በፊት እግዚአብሔር ከሁሉ በላይ ነበር እርሱ መጀመሪያ ሃሌሉያ ( 2x) ለነበረው ላለው ለሚኖረው ሕያው አምላክ ልዑል እግዚአብሔር የሰራችሁ ፍጥረታት በሙሉ በመገዛት አሜን ክበር በሉ ( 2x) የውሃው ክምችት ሳይባል ባሕር መጀመሪያ እግዚአብሔር ነበር ምድርም ሳታበቅ ቡቃያና ሳር አስቀድሞ እግዚአብሔር ነበር ሳይለዩ ገና ውሃና መሬቱ እግዚአብሔር አለ በኃይል በችሎቱ እለታት ዓመታት ዘመናት ሳይሆኑ እርሱ እንዳለ አለ በክብር ዙፋኑ አዝ፦ በመጀመሪያ እግዚአብሔር በመጀመሪያ በመጀመሪያ የእኔ አምላክ በመጀመሪያ ከሁሉ በፊት እግዚአብሔር ከሁሉ በላይ ነበር እርሱ መጀመሪያ ሃሌሉያ ( 2x) ሳይሰራ አዳም ሳትመጣ ሄዋን መጀመሪያ እግዚአብሔር ነበር እፍ ሳይልበት ገና እስትንፋሱን አስቀድሞ እግዚአብሔር ነበር ሳይባሉ ገና ብዙ እና ተባዙ ምድርን አስተዳድሩ ፍጥረታትን ግዙ አዳም ሕያው ሆኖ ሳይመላለስ በማደሪያው አለ የክብር ንጉሥ ስሙም ቅዱስ አዝ፦ በመጀመሪያ እግዚአብሔር በመጀመሪያ በመጀመሪያ የእኔ አምላክ በመጀመሪያ ከሁሉ በፊት እግዚአብሔር ከሁሉ በላይ ነበር እርሱ መጀመሪያ ሃሌሉያ ( 2x) ለነበረው ላለው ለሚኖረው ሕያው አምላክ ልዑል እግዚአብሔር የሰራችሁ ፍጥረታት በሙሉ በመገዛት አሜን ክበር በሉ ( 2x)