የልዑሉ አምላክ ማደሪያ አካሉ የሆንሽ የእርሱ መኖሪያ አንች ቤተክርስቲን ተነሺ የሰጠሽን ተስፋ አትርሺ ሁኝ እንጂ ልክ እንደ ሙሽራ ልትቆሚ እኮ ነው በተራራ የሰርግሽ ቀን በጣም ቅርብ ነው ሙሽራሽ ደጂ እያንኳኳ ነው ዘምሪለት እንጂ በዕልልታ የምን በራድ ትኩስ ለብታ ድመቂ ንሺ ተቀደሽ ሙሽራይቱ ሆይ ተነሽ መቅረዝሽ በዘይት ይሞላ በር እንዳይዘጋብሽ ኋላ ቀን ሳላ ዛሬ ተዘጋጂ በፍጻሜው እንዳትጐጂ ረሻሽ ወይ ጌታሽ መመለሱን ጠብቂኝ እመጣለህ ማለቱን መዘናጋቱ ምነው በዛ ጣል እረግሽው ልክ እንደዋዛ የወደፊቱ ክብር ተስፋ ተጋረደ ከዓይንሽ ስር ጠፋ ጊዜው ደርሷል እባክሽን ንቂ ቤተክርስቲያን ተጠንቀቂ ሊያደርግሽ ፍሬ አልባ ገለባ የዓለም ኮተት ሰርጐ ገባ ተኝተሽ ጠላት ዘሩን ዘራ ምድርሽ እንክርዳድን አፈራ በበጉ ደም ፈጥነሽ ታጠቢ አስታውሺ ተስፋሽን አስቢ የሰርጉ ቀን በጣም ተቃርቧል ሙሽራሽ ወደ አንቺ ይመጣል አሜን ማራናታ ቶሎ ና የምትይበት ጊዜው ነውና ይሰማ ድምፅሽ ያስተጋባ ወደ ልዑል ማደሪያ ይግባ ከእንግዲህ በምድር ምን ቀረሺ ናፍቂ ወደሰማይ ገስግሺ ይልቃል በዚያ ያለው ደስታ ማሰማት ዝማሬና ዕልልታ በዚያ እኮ ርሃብ ጥማት የለም ደዌ ህመም አይታወቅም እንባ ከዓይኖችሽ ይታበሳል በጉ የአንች እረኛ ይሆናል የበጉ መሽራ አንቺ ሆይ ይህ ክበር አልናፈቀሽም ወይ ይመጣል ወዳጅሽ ወደ አንቺ ተነሽ ቁሚ ተዘጋጂ ማራናታ ማራናታ አሜን ጌታ ሆይ ተሎ ና አሜን ኢየሱስ ተሎ ና አሜን ጌታ ሆይ ተሎ ና አሜን ኢየሱስ ተሎ ና (2x)