ሃይልህ እጅግ ታላቅ ነው ሁሉንም ይችላል በምድረ በዳ ላይ መናን ይመግባል ምልክት ሳይታይ ዝናብን ይሰጣል ተስፋ ያረጉትን ሁሉ ያሳርፋል በመከራዬ ቀን ቀድሞ ያገኘኝ ከሁሉ ፈጥኖ የደረሰልኝ በወጀብ ባውሎ መሃል መንገድ ያለው እኔ ማመልከው ጌታ እግዚኣብሄር ነው ውሃም የብሱም ሁሉ መንገዱ ነው ምስኪኑን ስታስብ ቁልፉ በእጅህ ነው ማን ይገምተዋል ጌታ አመጣጥህን ከጉድ ታወጣለህ ገልጠህ ማዳንህን ደመናን ሰንጥቆ ቀዶ የሚመጣ ቢያሻው መንገዱ ነው ተራምዶ ሊመጣ እኔን ያስብ እንጂ ምንም ማያግደው እርሱ ከፈለገ ውሃ መንገዱ ነው ማይታለፍ መስሎ የቆመ ተራራ ነጎድጓዱ ቃልህ ሲመጣ እያስፈራ የብረቱን መዝጊያ ያይንህ ጨረር ከፍቶት ቀጥ ባለው መንገድ አለፍን ክብርህ መርቶን