ወደ ደጆቹ በመገዛት እገባለሁ ባደባባዩ በምስጋና እታያለሁ ወደ መቅደሱ በአምልኮ እዘልቃለሁ ስሙን ሳነሳ ሳወድሰው መች ጠግባለሁ በእውነተኛ ቃሉ አስቦ የወለደኝ የድካሙ ፍሬ የደሙም ዋጋ ነኝ በለመለመ መስክ ሁሌ የሚያሰማራኝ ገና ከፍጥረትም የእጆቹ ስራ ነኝ ነፍሴ ሃጢያቷ ተነስቶላት ደስ ብሏታል የክስ መዝገቧ ተገልብጦ ደስ ብሏታል መካከለኛው ከመሃል ገብተህ ደስ ብሏታል የጥል ግድግዳን በደምህ አፍርሰህ ደስ ብሏታል ባንተ ደስ ይለኛል ሃሴት አድርጋለሁ ምንም በእጄ ባይኖር ባንተ እደሰታለሁ ከወይን ጥጅ ይልቅ ፍቅርህን አስባለሁ ሁሉም ቢሞላልኝ ተመስገን እላለሁ መች ጠግባለሁ ሳወድሰው እኖራለሁ ደስ ደስ እያለኝ እግዚኣብሄርን አመልካለሁ ደስ ደስ እያለኝ ለልኡሉ እገዛለሁ በብዙ ደስታ ወደፊቱ እገባለሁ ሁሌ ሳመልከው ሳስደስተው እኖራለሁ