ኑሮ ያለጌታ ታቅቶኝ ኀጢአቴ አስመርሮኝ ወደ ኢየሱሴ ብመለስ የእርሱ ደግነት ማርኮኝ በድል ጐዳና ብገባ ፍቅሩ ነፍሴን ብትፈታ ጉልበቴን ለጠላት ላልሰጥ ቃል ገባሁኝ ለጌታ በመከራና በጭንቀት እሮሮ ጌታን አመልከዋለሁ ኑሮ ያለእርሱ ጉዳት ነው ከእርሱ ጋር ግን ደስታ የመልካም ሁሉ መሰረት ይመስገን የእኛ ጌታ ስንጨነቅ የሚራራ ስንደክም ደጋፊያችን በበረሃ ዓለም እያለን ስንጠማ እርካታችን ዞሮ ምግቢያችን ኢየሱስ ማረፊያችን አንተ ነህ ብንከዳህ አያዋጣንም የድሃ ጐጇችን ነህ ጌታ ጌታችን ጌታችን አስታውሰን ብለን ተጣርተን ሳናፍር እስካሁን ተጉዘናል በነገር ሁሉ መጽናትን ከጌታ ተምረናል የሚያሳፍር ስም አይደለም የሰጠኸን ጌታችን ክርስቲያን ጀግንነት እንደው ይረዳል ነን ልባችን ክፉውን ሁሉ ተቃውመን ከኀጢአት ጋራ ታግለን ጉዟችን በድል ያከትማል የጌታን መስቀል ይዘን ክብር ክብር ሃሌሉያ (2x) የነፍሳት ሁሉ ምሥጋና ዙፋንህን ይክበበው በቸርነትህ ተገርሟል በልጅህ የዋጀኸው (2x)