ልደቱ በረት ሞቱ በመከራ እንጨት ላይ ዕድሜውን ፈጅቶ በስቃይ ለማልጠቅመው ለእኔ ጌታ እራሱን ጐዳ ፍርድ ተሸክሞ ወደ ሞት ተነዳ አዝ፦ ምን ደላው ለእርሱ ምን ደስ አሰኘው የመስቀል ላይ ጣሩ እንደምን ማቀቀው አዬ ፍቅር ሆኖ ሞተ እንደተገፋ የእሾህ አክሊል ጭኖ አለ አንገቱ ደፋ (2x) ፍቅርን ለብሶ ርህራሄ አስገድዶት የነፍሴ ለቅሶ ተሰምቶት መጣ የእኔ ጌታ ሞተ ተጐሳቁሎ የአባቱን ፍቃድ ፈጽሞታል ታግሎ አዝ፦ ምን ደላው ለእርሱ ምን ደስ አሰኘው የመስቀል ላይ ጣሩ እንደምን ማቀቀው አዬ ፍቅር ሆኖ ሞተ እንደተገፋ የእሾህ አክሊል ጭኖ አለ አንገቱ ደፋ (2x) ምን ዋልኩለት ለእዚህ ወዳጅ ከቶ ለሞተው እኔን ተክቶ አልተገራም ልቤ አልታረቀም ገና መቼም ተስፋ አልቆርጥ ቀን ይመጣልና አዝ፦ ምን ደላው ለእርሱ ምን ደስ አሰኘው የመስቀል ላይ ጣሩ እንደምን ማቀቀው አዬ ፍቅር ሆኖ ሞተ እንደተገፋ የእሾህ አክሊል ጭኖ አለ አንገቱ ደፋ (2x)