አነባ ጌታዬ አፈር ላይ ተደፍቶ የወደቀበትን ጭንቀት ተመልክቶ ጌታዬ ተጨንቆ አባዬ ሆይ አለ አጋዥ አልተገኘም ለጌታ የዋለ መስቀል ተሸክሞ ትከሻው ተላጠ ግርፋቱ በዛ ገላው ተመለጠ ራቁቱን ደም ሲያፈስ በቀራንዮ ዋለ አንገቱ ደፋ ሲል እዳ ተከፈለ አዝ:- ጌታዬን አከብራለሁ (3x) በኑሮዬ (2x) ዝናን ከበሬታን ሞገስን በሥጋ ሊያገኝ ወዶ ነፍሱን ከአለም ከሚያስጠጋ ይሻላል ጭንጋፉ ውዳቂ እኔን መሳይ በስጋው ተንቆ በእምነት ጌታን የሚያይ( ጌታዬን አከብራለሁ (3x) በኑሮዬ (2x) ማቅቆ በመከራ ጐስቋላ አካል ይዞ በረሃን የሚዘልቅ ጌታን ተመርኩዞ ተሽማቆ ኑሮን ለጌታ ሲል ችሎ ያለፈን አየሁት አክሊል ተቀብሎ አዝ:- ጌታዬን አከብራለሁ (3x) በኑሮዬ (2x) በሞቱ ሊመስለው ጌታን ተከትሎ ወድቆም የሚነሳ አልሸነፍ ብሎ ለጠላቱ ታግሎ የማታ የማታ ጌታው ምሎለታል እርሱ እንደሚረታ አዝ:- ጌታዬን አከብራለሁ (3x) በኑሮዬ (4x)