በዚያም በታላቁ ቀን ኢየሱስ ቆሞ ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ በእኔ የሚያምን መጽሐፉ እንዳለው የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል ዛሬም ይሄ ነው ፀሎታችን የእምነት ቃሉን የሰጠ እስከ ፍጻሜው ታማኝ ነው የፍጥረት ሁሉ አባት ለልጆቹ የሚዋጋው እሩህሩህ አምላኬ የፍቅር ውኃ ምንጭ ኃጢአት እንዳይጥለኝ ያዝከኝ በቸርነት አዝ፦ የሕይወት ውኃ ምንጭ የነፍስ ሁሉ እረኛ ያንቀላፋው ልቤ በውሃው ይነሳል አፍስስ ቅዱስ መንፈስህን ለተጠማች ነፍሴ ይፍለቅ ፍቅርህ ከሕይወቴ ይህ ነው ፀሎቴ ማንም የተጠማ ቢኖር ወደኔ ይምጣ ብለሃል የሕይወት ውኃ ወንዝ በሰው ሁሉ ላይ ያድራል የመንፈስ አንደበት የሰማያት እንባ ፈሰሰ ከዓይኔ መቼም ላልጠማ አዝ፦ የሕይወት ውኃ ምንጭ የነፍስ ሁሉ እረኛ ያንቀላፋው ልቤ በውሃው ይነሳል (ማንም ለተጠማ የምትሰጥ እርካታ) አፍስስ ቅዱስ መንፈስህን ለተጠማች ነፍሴ ይፍለቅ ፍቅርህ ከሕይወቴ ይህ ነው ፀሎቴ የሕይወት ውኃ ምንጭ በውኃው ይነሳል አፍስስ ቅዱስ መንፈስህን