Song Lyrics

ታሪክ

Sofia Shibabaw
Sima Belew
ሰው ማነህ አይባል ሳይባል ነኝ ይላል ከስሙ አስቀድሞ ያለ የሌለ ነገር ጨማምሮ ይናገራል ሥራህስ ምንድን ነው ብለው ቢጠይቁት አሳምሮ ያወራል ያብራራል ከሰሙት ለመጥምቁ ዮሐንስ ኢሄ እድል ደረሰው አንተ ማነህ ብሎ ብዙ ህዝብ ጠየቀው እንዲህ ሲል መለሰ ስለ ማንነቱ ሳያፍር ገለጠ እውነትን ከውሸቱ እኔ ጠራጊ ነኝ ድምጽ ነኝ ምጮኸው መንገድ የማዘጋጅ ከኋላ ሄዳለሁ አይደለሁም ኤልያስ ከነብያቶች አንዱ የማመቻች ነኝ ጥርጊያ ለመንገዱ አላቸው መልሶ ራሱን አሳንሶ የጫማውን ጥፍር ልፈታ የማይገባኝ ከእርሱ አንሳለሁኝ እኔ ላንስ ይገባል እርሱ ከእኔ ይበልጣል እኔ በውኃ ሳጠምቅ በእሳት ያጠምቃል እርሱ ከእኔ ይበልጣል[1][2] እንዲህ ነው እንግዲህ ትህትና እንዲህ ነው እንግዲህ ዝቅ ማለት (2x) ራስን ማወቅ ማንነትን ሰው መሆንን መረዳትን ያበዛዋል መዋረድን ሒሳቡ ደግሞ ኢሄ ነው ዝቅ ያለ ነው ከፍ የሚለው (2x) እኔ (6x) ባልኩኝ ቁጥር እወጣለሁኝ ካለሁበት አጥር እኔ (6x) ያልኩኝ ለታ ያበቃልኛል የማታ የማታ እኔነቴ መድከሚያዬ እኔነቴ መውደቂያዬ እኔነቴ መወጫዬ እኔነቴ መቃብሬ ስንቱ ተቀበረ በእኔነት መቃብር ትንሳዔ ያምጣለት ትሁቱ እግዚአብሔር (2x) እንደ እንጀራ አይለመን ትህትና መለወጥ ነዉ መወሰን ነዉ የሚያስፈልገዉ በትዕቢት ከጋሉ እኔነቴ መድከሚያዬ እኔነቴ መውደቂያዬ እኔነቴ መወጫዬ እኔነቴ መቃብሬ
Mezmur debter

Ethio Christian Lyrics Collection