አዝ፦ የዚህ ዓለም ኑሮ ምድረበዳ የማይደፈን ቀዳዳየማይደፈን ቀዳዳ ቋጡ ጠብ አላለም ጉድጓዱም አልሞላ አንዱን ስንሸኘው ከተፍ ይላል ሌላው እንቆቅልሹ ሺህ ችግሩም እልፍ ነው ጌታን አምነን እርፍ ነው ጌታን ይዘን እርፍ ነው ጌታ ካለ እርፍ ነው ልንደላደል ልንመቻች ቀን ሙሉ ስንሮጥ እላይ እታች መቼ ሞላልን እንዲህ እየጣርን ነፍሳችን እረፍት አጥታ ፀሐይ ማዘቅዘቋን መምሸቱን አውቀን ወደ እግዚአብሔር ጉያ እንግባ ፈጥነን አዝ፦ የዚህ ዓለም ኑሮ ምድረበዳ የማይደፈን ቀዳዳየማይደፈን ቀዳዳ ቋጡ ጠብ አላለም ጉድጓዱም አልሞላ አንዱን ስንሸኘው ከተፍ ይላል ሌላው እንቆቅልሹ ሺህ ችግሩም እልፍ ነው ጌታን አምነን እርፍ ነው ጌታን ይዘን እርፍ ነው ጌታ ካለ እርፍ ነው በመሸማቀቅ በሰቀቀን በሃሩር ፀሐይ በእኩለ ቀን ውኃ ፍለጋ ከአድማስ ወዲያ የተጓዘችው በሰማሪያ አምስቱም ባሎቿ ያልሰጧትን ደስታ ኢየሱስን ስታገኝ ቋጠሮዋ ተፈታ አዝ፦ የዚህ ዓለም ኑሮ ምድረበዳ የማይደፈን ቀዳዳ ቋጡ ጠብ አላለም ጉድጓዱም አልሞላ አንዱን ስንሸኘው ከተፍ ይላል ሌላው እንቆቅልሹ ሺህ ችግሩም እልፍ ነው ጌታን አምነን እርፍ ነው ጌታን ይዘን እርፍ ነው ጌታ ካለ እርፍ ነው እንድንጮህ አባት አባት ብለን እግዚአብሔር ሰጠን መንፈሱን በሰማይም ቤት ሰርቶልናል በቅርቡም መጥቶ ይወስደናል ወላጅ አልባ ልጆች አይደለንም እኛ ጌታችን በክብር ይመጣል ዳግመኛ አዝ፦ የዚህ ዓለም ኑሮ ምድረበዳ የማይደፈን ቀዳዳ ቋጡ ጠብ አላለም ጉድጓዱም አልሞላ አንዱን ስንሸኘው ከተፍ ይላል ሌላው እንቆቅልሹ ሺህ ችግሩም እልፍ ነው ጌታን አምነን እርፍ ነው ጌታን ይዘን እርፍ ነው ጌታ ካለ እርፍ ነው የቤተልሔም ረሃብ ያልፋል ወደ ሞአብስ ምን ያለፋል ያለመጠበቅ ያለማረፍ ለመዘረፍ ነው ለመገፈፍ እግዚአብሔር ሕዝቡን በርግጥ ይጐበኛል ሁሉም ሰው በጊዜው ዳኝነት ያገኛል አዝ፦ የዚህ ዓለም ኑሮ ምድረበዳ የማይደፈን ቀዳዳ ቋጡ ጠብ አላለም ጉድጓዱም አልሞላ አንዱን ስንሸኘው ከተፍ ይላል ሌላው እንቆቅልሹ ሺህ ችግሩም እልፍ ነው ጌታን አምነን እርፍ ነው ጌታን ይዘን እርፍ ነው ጌታ ካለ እርፍ ነው